ሰው በተፈጥሮው አንድ አይነት ዑደትን የመውደድ ባህሪይ አለው ፤ ጠዋት ፀሐይ ትወጣለች ፣ ማታ ደግሞ ትጠልቃለች ፣ በዓመት አንዴ የዝናብ {ክረምት} ወቅት ይመጣል ከዚያም ይሄዳል … አንድ ዓይነትነት !
እነዚህ የለመድናቸው ሁኔታዎች ለወጥ ሲሉ ግር ይለናል ፤ ይህ ስሜት ደግሞ በትክክለኛው መጠን መኖሩ የጤናማነት ምልክት ነው ፤ ነገር ግን ምንም ዓይነት ለውጥን ፈጽሞ የማንፈልግ ከሆነ የ“ፎቢያ” ችግር ሊኖርብህ ይችላል፡፡
የለውጥ “ፎቢያ”የአንድን ሰው የመኖር ጉጉት የሚሰርቅ የፍርሃት አይነት ነው ፤ የዚህ ፍርሃት ተጠቂዎች በኑሮ ደረጃቸው ፣ በእውቀት አለማቸው ፣ በንግዱና በስራ መስካቸውም ሆነ የሚኖሩበትን ስፍራና ሁኔታ አስመልክቶ ምንም ዓይነት ለውጥ የማድረግ ፍላጎቱም የላቸው ፤ ከመጣም ለውጡን አጥብቀው ይቋቋሙታል፡፡
በአጭሩ ምንም ዓይነት ነገር ከቁጥጥራቸው ውጪ እንዲሆን ስለማይፈልጉና ለውጥ ደግሞ ያንን ሁኔታ እንደሚፈጥርባቸው በማሰብ ስለሚፈሩ ባሉበት ሁኔታ ኖሮ ማለፍን ይመርጣሉ፡፡
ዙሪያችን ተለውጦ ሳለ አለመለወጥ ፣ የእድገት እድል እያለ እንኳን መኖሪያን ፣ ስራንና የንግድ ዘርፍን መቀየር መፍራት ፣ ለማደግ አለመፈለግና የመሳሰሉት ጠንቆች የዚህ ፍርሃት ሰለባዎች ችግር ናቸው፡፡
ለማስታወስ ያህል …
• ለውጥን በጥንቃቄ አይን ማየትህ ትክክለኛ የለውጥ ምላሽ መሆኑን አስታውስ፡፡
• ወደድክም ጠላህም ለውጥ የሕይወትህ አካል መሆኑን አምነህ ተቀበለው፡፡
• አንተ የለውጥ እርምጃ ወሰድምክ አልወሰድክ ፣ ለውጥ መምጣቱ አይቀርም፡፡
• ለውጥ በራሱ ሲመጣም ሆነ፣ ለውጥ በአንተ አነሳሽነት ሲከናወን ከለውጡ ጋር አብረህ መራመድ ለስኬታማነትህ ወሳኝ ነው፡፡
• ከለውጥ ጋር የሚመጣ የማይመች ስሜት ጤናማ ፣ ትክክለኛና ሁሉም ሰው የሚጋራው ስሜት መሆኑን አትርሳ፡፡
ራዕያችሁን ማወቅና ያንን መከተል ነባሩን አሰልቺ ሂደት በመቀየር ወደ አዲስ ለውጥ የሚያሸጋግር አስገራሚ ልምምድ ነው፡፡
ራሳችንን እንፈትሽ ፡ ራሳችንን እንመልከት።
ይቀላቀሉ ለቴሌግራም t.me/danelroza
