ብዙዎቻችን የምንኖረው በሁለት ሙት ዓለማት ውስጥ ነው። አንደኛው “የትላንት ጸጸት” ሲሆን ፣ ሁለተኛው ደግሞ “የነገ ስጋት” ነው።
ትላንት የቱንም ያህል ብትሳሳት ፣ ዛሬ ያንን ስህተት የመቀየር አቅም የለህም። ነገ ደግሞ የቱንም ያህል ብትጨነቅ ፣ ገና ያልመጣን ሰዓት ልትቆጣጠር አትችልም።
ያለህ ብቸኛው ሀብት “አሁን” ነው ! ![]()
ዛሬን የምትኖርበት መንገድ የትላንት ቁስልህን ይፈውሳል፤ የነገውንም መንገድ ይጠርጋል።
ለዛሬ ፫ ወርቃማ መመሪያዎች ፦
፩. ትላንትን በሰላም ሸኘው
፦ “እንዲህ በሆነ ኖሮ” የሚለው ሃሳብ የዛሬን ጉልበትህን እንዲሰርቅህ አትፍቀድ። የሆነው ሆኗል፤ ትምህርቱን ውሰድና በሩን ዝጋ።
፪. ነገን ለፈጣሪ ስጠው
፦ ነገ ምን እንደሚፈጠር ማሰብህ ዛሬን እንድትደሰት አያደርግህም። ዛሬ የምትዘራው ዘር ነገ መልካም ፍሬ እንደሚያፈራ ብቻ እመን።
፫. በአሁኑ ሰዓት ንቁ ሁን
፦ አሁን የያዝከው ስልክ ፣ አሁን የምትተነፍሰው አየር ፣ አሁን ያለህ እድል ትልቁ ስጦታህ ነው።
ዛሬን በትክክል ከኖርክ ፣ ነገ ራሱን ችሎ ይስተካከላል።
ያንተ “አሁን” የጀመረው በዚህ ሰከንድ ነው! ምን ለማድረግ ወሰንክ ?
ይቀላቀሉ ለቴሌግራም
👇👇👇
http://t.me/danelroza
ለፌስቡክ
👇👇👇
http://fb.com/danelroza
ለሊንክደን ፡
👇👇👇
linkedin.com/in/danelrozlroza
